Showing posts with label እይታ. Show all posts
Showing posts with label እይታ. Show all posts

Tuesday, February 25, 2014

መናፍቃን ፕሮቴስታንቶች፤በኦርቶዶክሳውያን ክርስቲያኖች ክፍል 2

                                                                                                         ከሣቴብርሃን ገ/ኢየሱስ
እንግዲህ ወደ ጥንተ ነገሩ እንመለስና መናፍቃኑ ለዚህ እኩይ አላማቸው መሳካት የሚጠቀሟቸውን ህቡዕ ስትራቴጂዎች እንመልከት፡፡ ምልመላ፡- የጉድ ሙዳዮቹ ወደ ት/ቤቱ አዲስ የተቀላቀሉ የ11ኛ ክፍል ተማሪዎችን ዋነኛ ኢላማ አድርገው በአዲስ አመት አዲስ ክህደት፤አዲስ ብልጠት ፤ለአዲስ... ‹‹ታርጌት›› ይዘው ብቅ ይላሉ፡፡ ይበልጥ ወደ መጤዎቹ ያተኩሩ እንጂ ነባር 12ኞችን መከታተላቸው ያው አይቀርም፡፡ ለኑፋቄ ጦርነት የሚዘምቱባቸውንም ተማሪዎች የሚመለምሉበት የራሳቸው
 የሆነ መስፈርት አላቸው፡፡ የጠለቀ ነገረ ሀይማኖትም ሆነ የምግባር እውቀት የሌለው፤ለሐይማኖቱ ባይተዋር የሆነሠ፤ከቤተክርስትያን የራቀ የማያስቀድስ የማይፆም፤ የማይፀልይ፤ከአባቶች እግር ስር የራቀ፤በስጋ ፈቃድ የወደቀ፤ከቅዱሳት መፃህፍት ያልተጣበቀ ብቻ በእነሱ አስተሳሰብ ብዙ የማይፈትናቸው ሌበራል ክርስቲያን ብጤ ቀዳሚ ምርጫቸው ነው፡፡
ወጥመዶች፡-
የምልመላውን ስራ በስውር ከጨረሱ በኋላ ወደ ስራው በቀጥታ ይሰማራሉ፡፡ ስራውን አሀዱ ብለው የሚጀምሩት እንደማግኔት የየዋሀኑን ልብ ከየአቅጣጫው ከሳበ በኋላ መፈናፈኛ በማሳጣት አጣብቆ እና አንቆ የሚይዝ ወጥመድ መዘርጋት ነው፡፡ ይህ ‹‹ኦፕሬሽን›› በሁለት ነገር ምክንያት በአብዛኛው ይሰካላቸዋል፡፡ ወጥመዶቹ በመንፈሳውያን እይታ ካልሆነ በስጋዊ እይታ የማይታወቁ ብዙዎች እንደ ቀላል የሚያይዋቸው ሳይታወቁ የማጥቃት ሀይል ያላቸው በመሆኑ የሀይማኖት ብሎናቸው የላላ ዝንጉ ተማሪዎች በቀላሉ ይቀበሉታል፡፡ በተጨማሪ አጥቂው ቡድን የተሟላ አደረጃጀት፤የካበተ ልምድና በቂ ስልጠናን ስለወሰደ በብልጠትና በማታለል ስራ የብዙዎችን ልብ ወደ ወጥመዶቹ ይገፋል፡፡ ነገሩን ቅኔ አደረኩት መሰል ወጥመድ የተባሉትን እስቲ
እንያቸው ፡-
1.የመናፍቃንን መዝሙር መስማት፡-
መዝሙር ስላደረገውና ስላላደረገው ስለሚያደርገውም ነገር እ/ር የሚመሰገንበት ሀሌታ፤መሻታችንን የምንጠይቅበት ጸሎትም ጭምር ነው፡፡ ኦርቶዶክሳዊት ቤ/ክ ፈጣሪዋን የምታመሰግንበት የራስዋ ህግና ስርአትአሏት፡፡ ሁሉ በህግና በአግባብ በስርአትም
እንዲሆን ታዘናልና፡፡ (2ቆሮ 14፡10) በዜማ ደረጃ በአንፃረ ያሬድ በተረከብው ጥዑም ሰማያዊ ዜማ ‹‹ ለኢትዮጵያዊያን ምግባቸውን ሰጠሃቸው›› (መዝ.74፡14 ) የሚለው ቃለ ትንቢት ይፈፀም ዘንድ ግዕዝ፤እዝል፤አራራይ የተባሉትን የመላእክት እንጀራዎች እየተመገብን እንኖራለን፡፡ በንዋያት ደረጃ አባቶቻችን ቅዱሳን አበው፤ቅዱሳን ነቢያት፤ካህናት በዘመሩባቸው በቅብዓ ሜሮን ከበረው እግዚአብሔር ንብረት በሆኑ ንዋያትበበገና፤በመሰንቆ፤በፀናፅል፤በመቋሚያ፤በከበሮ በመሳሰሉት ለምስጋና እንተጋለን፡፡ ተመልማዮቹ ሌበራል ክርስትያን ተማሪዎች ይህን የአባቶች ስርአትና ትውፊት በቅጡ አያውቁትም፡፡ በኦርቶዶክሳዊ መዝሙር ለመንፈሳዊነት ሳይሆን በዳንስና ዘፈን ለዓለማዊነት ያጋደሉ ናቸው፡፡ ይህን ስስ ብልታቸውን ተመልክተው መናፍቃኑ ወትሮም ያዘመሙ ተማሪዎችን በአንደኛው ወጥመድ እንዲወድቁ ያደርጋሉ፡፡ ይኸውም የራሳቸውን ዘፈናዊ መዝሙር እንዲያደምጡ ማድረግ ነው፡፡ በክፍል ውስጥ፤በግቢ አካባቢ ሲንቀሳቀሱ፤ካፌ ሲሄዱ ወደጫካ ሲሄዱ፤በቡድን አሳይመንት ሲሰጥ ሰብሰብ ሲሉ ብቻ በአገኙት አጋጣሚ እያንጎራጎሩ የ ‹‹ፕሮሞሽን›› ስራ ይሰራሉ፡፡ ቀስ በቀስ እንጉርጉራቸው መወደድ ዜማቸው ቀልብ መሳብ ይጀምራል፡፡ መቼስ አንድ ክፉ ሰው ባልንጀራውን በመርዝ ሊገድለው ቢፈልግ ተስገብግቦ ጣፍቶት ተሻምቶ ሲበላው አንፈርፍሮ ሚገድለው ተወዳጅ ምግብ ውስጥ እንጂ ገና እንዳየው የሚያቅረው እሬት ውስጥ መርዙን
አይጨምርም፡፡ ሰይጣንም እንደዚሁ ነው በየዘመናቱ የሚያስነሳቸውን መናፍቃን ተጠቅሞ የክህደት ዘሩን ለመዝራት ሰዎች
በሚወዱትና በሚደሰቱበት ግን ከንቱ በሆነ ነገር ገብቶ ማሳት ልማዱ ነው፡፡ ‹‹ወልድ ፍጡር በመለኮቱ›› ያለ የመናፍቃን አለቃ አርዮስ ይህን ኑፋቄውን ሲያስፋፋ የነበረው እንዲሁ በደረቁ አልነበረም፡፡ በነበረው የግጥም የመፃፍ ችሎታ ተጠቅሞ የሀሰት ትምህርቱን በየስንኞቹ እየሰገሰገ በዘመኑ ግጥም ወዳድ ለነበረው ማህበረሰብ በተነው፡፡ በቀላሉ
ተቀባይነትንም አግኝቶ በግጥም ቀጭን መንገድነት ሾልኮ በምእመናኑ ልብ ላይ ከነህፀፁ ጉብ አለ፡፡
ዳግመኛ ‹‹ ድንግል ምርያም የወለደችው ሰው ነው ›› ያለው ከአርዮስ የማይተናነሰው የፓትርያርክ መናፍቅ ንስጥሮስ ንግግር አሳማሪና ድምፀ መልካም እንደነበር ይነገርለታል፡፡ ብዙዎች አንደበተ ርቱዕነቱን በማድነቅ አውቀውም ሳያቁትም ተከትለውታል፡፡
በስነ-ፅሑፍና በአንደበተ ርዕቱዕነት ማዳበሪያ ተጠቅሎ ያለን ክህደት ተጭነው ሲነዱ የነበሩ የዳቢሎስ አህዮች አርዮስና ንስጥሮስ ቢሞቱም ነጅው ከነጭነቱ በየዘመን ስለይቀያየር ማዳበርያ ብቻ ቀይሮ ለዘመነኞቹ ተተኪ አህዮች መናፍቃን አስጠግርሯቸዋል፡፡ በዚህ ዘመን የዘፈን ምርኮኛ ያልሆነ ወጣት ብናገኝ እድለኞች ነን፡፡ ስለዚህ አጅሬ ይህችን አጋጣሚ ተጠቅሞ የዘፈን ምት፤የዘፈን ቃና፤ዘፈን ቀለምናሽታያላቸው በስም ግን መዝሙር የተባሉ መናፍቃን መዝሙሮችን ማምረት ማስመረት ጀመረ፡፡ ወጣቱ መንፈሳዊ
ተብለው የሚሰጡት ስመ-መዝሙሮች ዓለምን ካሳበዱ ዘፈን ስልቶች ከነ HIPHOP,JAZZ,REGEE,RAP… ጋር
ተስማማለትና ወደደው፡፡ ነገሩ መላ ያጣ ከመሆኑም የተነሳ ገና በኢትዮጵያ ድምፃውያን ያልተሰራበት ረቀቀ የባህር ማዶ የዜማ ስልት ቀድሞ በፕሮቴስታንት ዝማሬ ላይ እናገኘዋለን፡፡ እንደው ዛሬ በስንቶቻችን ሞባይልና ላፕቶፕ ላይ የመናፍቃን መዝሙር ይገኛል ?
አላስተዋልነውም እንጂ ብዙዎቻችን ወደ ወጥመዱ እየተጠጋን ነው፡፡ ባለፍን ባገደምን ቁጥር አለፍ ስንል ለምንሰማቸው እልፍ መዝሙሮች አንገት ጭንቅላት ነቅነቅ፤መሰጥ፤ሰረቅ፤መጠቅ የምንል ወሰድ መለሶች ሆነናል እኮ ! ከወጥመድ አንድ ያልተነካካን ስንቶቻችን እንሆን ?
ስለሆነም በፍፁም የእነሱን መዝሙር እንዳንሰማ አደራ እላችኋለው፡፡ የእኛም የእነሱም አንድ ነው ካላችሁ ፍፁም ተሳስታችኋል፡፡ እነሱ ከሐዲያን ናቸው የከሀዲ መዝሙር ደግሞ አናደምጥም፡፡
ድንግል ማርያምን የቀደሰ ያወደሰ መዝሙር በሰማንበት ጆሮ እሷን የካዱ የሙታንን መዝሙር ከምናደምጥበት ቢደፈን ይሻላል፡፡
ስለሃዋርያት፤ፃድቃን፤ሰማ ዕታት፤መላዕክት፤ሊቃውንት ውዳሴና
ክብር የሚናገር መዝሙር በአንቆረቆርንበት ጆሮ እንዚህን ፈርጦች በካዱ ምልጃው ፀሎታቸው አይጠቅመንም ባሉ መናፍቃን አንደበት ተቀለፀ መዝሙር መስማት መናፍቅ
ከመሆን የማይተናነስ ሸፍጥ ነው !!
አስቡበት ይቀጥላል . . . . . . . .

መናፍቃን-ፕሮቴስታንቶች በኦርዶክሳውያን ተማሪዎች ክፍል1


 ከ ከሳቴብርሃን ገብረኢየሱስ

መናፍቃን በጌታ አነጋገር ፀራዊ(ክፉ ጠላት) በጌታ ደቀ መዛሙርት በሐዋርያት አነጋገር ቢፅ ሐሳውያን (ሀሰተኛ ባልንጀሮች) በሊቃውንት አነጋገር መናፍቃን ይባላሉ፡፡ ሊቃውንተ ቤ/ክ ለነዚ ከሐድያንይባላሉ ፡፡ሊቃውንተ ቤ/ክ ‹‹መናፍቅ›› የሚለውን ስም ሲሰጡ እንዲሁ በደፈናው አይደለም፡፡ ከነገረ ሃይማኖትም ሆነ ከምግባር ትምህርት ውስጥ ልቦናቸው የወደደውንና ከስጋ ፈቃዳቸው ጋር የሚዛመደውን በእነሱ መንገድ የሚሄደውን ብቻ ነጥለው የሚያምኑ ክፍሎ አማኞች ስለሆኑ ነው እንጂ፡፡ መናፍቅ ‹‹መ...ንፈቅ›› ኪሚለው ቃል የተገኘ ትርጉሙም-ክፋይ፤ እኩሌታ፤ አጋማሽ ማለት ነውና፡፡ በተለምዶ የፕሮቴስታንቱ አለም በዚህ ስያሜ ይጠራ እንጂ ከኦርቶዶክስ ተዋህዶ አምነት ውጭ ያሉ ብዙዎቹ ሃይማኖቶች የዚህ ስም ድርሻ ተጋሪዎች ናቸው፡፡ ለምሳሌ ሙስሊሞች ከአረማዊነታቸው ባሻገር መናፍቃንም ናቸው፡፡ እንዴት ቢሉ ከሚስጥረ ስላሴ የእግዚአብሄርን አንድነት ብቻ ነጥለው ተቀብለው ሶስትነቱን አያምኑም፤ አብ የባህርይ አምላክ እንደሆነ ሁሉ ቅድመ አለም ያለ እናት የወለደው የባህርይ ልጁ ወልድም አምላክ እንደሆነ አይቀበሉም፤‹‹ለሰማይ ደጅ ለአላህ ልጅ የለውም፡፡›› ብለው ያምናሉ እግዚአብሄር አዳምና ሄዋንን (አደም ና ሐዋን) አምላክነትን ፈልገው ባደረጉት አመፅ እንደረገማቸውና ከቀደመው ክብቸው እንደተዋረዱ ያምኑና ከ5500 ዘመን በኃላ ከልጅ ልጁ ተወልዶ እንደሚያድነው ለአዳም የሰጠውን የተስፋ ቃል፤ ኋላም ቃሉን ሳይረሳ ጊዜው ሲደርስ ወደዚህ አለም መጥቶ ተሰቅሎ እንዳዳነው የሚገልጸውን ነገረ ስጋዌውን ይክዳሉ፡፡ ስለዚህ ከፍሎ አማኞች (መናፍቃን) ናቸው፡፡ ካቶሊኮችም እንዲሁ ናቸው ኢየሱስ ክርስቶሰ ሥጋ ከመለኮት መለኮት ከሥጋ ተዋህዶ ሰው የሆነ አምላክ መሆኑን ያምናሉ፡፡ ዳሩ ግን ከኹለት አካል አንድ አካል ከኹለት ባህርይ አንድ ባህርይ መሆኑን ሽምጥጥ አድርገው ሲክዱ ይስተዋላል፡፡ ስለዚህ ከፍሎ አማኞች ናቸው፡፡ የዚህን ፅሑፍ ርዕስ ‹‹መናፍቃን-ፕሮቴስታንቶች…›› ያልኩበት ምክንያት ሌሎችም መናፍቃን እንዳሉ ለማጠየቅ ነው፡፡ የፅሑፉ ዋነኛ አላማ በተለይ በት/ቤ/ት አካባቢ ኦርቶዶክሳውያን ተማሪዎችን ከርትዕት- ሃይማኖታቸው አስኮብልለው የክህደት ደቀ-መዝሙር ሊያደርጋቸው ላይ ታች የሚራወጡ የመናፍቃን ፕሮቴስታንቶችን ክፉ ተግባር እንቃወም ዘንድ ማስቻል ነው፡፡ ቅድመ ልደተ ክርስቶስ 1000 ዓመት አስቀድሞ በሐልዎተ እግዚአብሔር የነበረውን ኋላም በዘመነ-ሐዲስ ከእስራኤል ቀጥሎ ክርስትናን በመቀበል መፅሐፍ ቅዱስን በራሱ ቋንቋ ተርጉሞ ለ2000 ዓመታት ያህል ወንጌልን ሲማርና ሲሰብክ እግዚአብሔርን ሲያመልክና ሲያስመልክ የኖረውን ፍጹም እምነት ያለው ክርስቲያን ደርሶ ወንጌል እንስበክባላችሁ ጌታን አልተቀበላችሁም ማለት‹‹ ለቀባሪው አረዱት›› እንደማለት ነው፡፡ በቤ/ክ ከጌታ ስም ይልቅ የቅዱሳን ስም ገኖ የሚጠራ ቤ/ክ በወንጌል ሳይሆን በባህል የምትመራ የሚመስላቸው የዋሃን ጥቂቶች አይደሉም፡ ቤ/ክ በገድሉ፤ በድርሳኑ ፤በመልካ መልኩ፤ በድጓው፤ በመፅሐፍቶቿ፤ በቅዳሴዋ፤ በማኅሌቷ ፤በሰዓታቷ በሁሉ ነገሯ ክርስቶስን ትሰብካለች፡፡ ቅዱስ ኤፍሬም የደረሰው ውዳሴ ማሪያም 63 በመቶ የሚናገረው ስለ ክርስቶስ መሆኑን ስንቶቻችን አናውቃለን? ትልቅ ነገር የተናገሩ ይመስል ‹‹ኢየሱስ ጌታ ነው! ››ብለው ጆሮአችን እስኪበጠስ ድረስ እንደ ብራቅ የሚጮሁብን ፕሮቴስታንቶች ቤ/ክ ክርስቶስን ‹‹የጌቶች ጌታ፤ የነገስታት ንጉስ፤ የአማልክት አምላክ›› ብላ ባሏት ሃብቶች ሁሉ እንደምታወደሰው ያውቁት ይሆን? ውሻ በጮኽ እቃ በወደቀ ቁጥር እየጠሩ የሚያንገላቱትን ኢየሱስ የሚውለን ስም በስምንተኛው ቀን ያወጣችለትን ድንግል ማርያምን ብናከብር እርሱንና ስሙን አላከበርንም ትላላችሁ? ብዙ ምሳሌ መደርደር ይቻል ነበር፡፡ነገር ግን የፌስ-ቡክ ፅሑፍና የግዢ እንጀራ ለቅምሻ እንጂ ለጥጋብ ስለማይሆን በዚሁ ልግታው፡፡
እውነታውና ሐቁ ይህ ሆኖ ሳለ ‹‹ወንጌል እንሰብካለን ፤ጌታን ተቀበሉ›› በሚል ጭንብል ክህደታቸውን ሸፍነው ኦርቶዶክሳዊያን ተማሪዎችን ከእውነት መስመር ለማስወጣት የሚማስኑ በተለይ በኛው ግቢ አሳላ ፕሪፓራቶሪ ት/ቤ/ት የሚገኙ ፕሮቴስታንቶች ችንደ አሸን በዝተው አሉ፡፡ አላማቸው ኑፋቄን ዘርቶ ማብቅል፤ኦርቶዶክስን ማዳከም፤ እንደ ፖለቲካ ፓርቲ የደጋፊ ቁጥር ማብዛት ስለ ሆነ ነው እንጂ እንደ ሐዋርያትና አርድዕት የወንጌል ማዳረስ ተልእኮ ቢኖራቸው ኖሮ አረማዊያን ሙስሊሞችን በሰበኩ ነበር ፡፡ በአንድ ወቅት አጼ ዮሐንስ አራተኛ ወንጌል እንሰብካለን በሚል ሽፋን ወደ ኢትዮጵያ ለመጡት ሚሲዮኖች የሰጡት ምላሽ ለዛሬዎቹ በሽተኞች ጥሩ መድኃኒት ነው፡፡ አጼ ዩሐንስ ለሚሲዎኖቹ እንዲህ ብለዋቸው ነበር፡፡ ‹‹እናንተ ወንጌል ለመስበክ የአህዛብን ሃገራት እነ ሊቢያን ፤እነ ቻድን ፤እነ ሱዳንን አቋርጣችሁ የክስቲያን ደሴት ኢትዮጲያ መጣችሁ፡፡ ቀልደኞች! በእውነት እናንተ ሰባኪያነ ወንጌል ብትሆኑ ኖሮ ሳውዲ አረቢያ ሄዳችሁ በሰበካችሁ ነበር››
ይቀጥላle